unfoldingWord 36 - የኢየሱስ መልክ ተለወጠ

unfoldingWord 36 - የኢየሱስ መልክ ተለወጠ

إستعراض: Matthew 17:1-9; Mark 9:2-8; Luke 9:28-36

رقم النص: 1236

لغة: Amharic

الجماهير: General

فصيل: Bible Stories & Teac

الغرض: Evangelism; Teaching

نص من الإنجيل: Paraphrase

حالة: Approved

هذا النص هو دليل أساسى للترجمة والتسجيلات فى لغات مختلفة. و هو يجب ان يعدل ليتوائم مع اللغات و الثقافات المختلفة لكى ما تتناسب مع المنطقة التى يستعمل بها. قد تحتاج بعض المصطلحات والأفكار المستخدمة إلى شرح كامل أو قد يتم حذفها فى ثقافات مختلفة.

النص

አንድ ቀን ኢየሱስ ሦስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ያዞ ሊጸልዩ ወደ ረጅም ተራራ ወጡ። ( ዮሐንስ የተባለው ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ያጠመቀው ሰው አልነበረም።)

ኢየሱስ በመጸለይ ላይ እያለ፣ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፣ በምድር ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ በጣም ነጭ ሆነ።

በዚያን ጊዜ ሙሴና ነቢዩ ኤልያስ ታዩ። እነዚህ ሰዎች በመቶዎች ከሚቈጠሩ ዓመታት በፊት በምድር ላይ ይኖሩ ነበር። በቅርቡ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ሞቱ ከኢየሱስ ጋር ተነጋገሩ።

ሙሴና ኤልያስ ከኢየሱስ ጋር በመነጋገር ላይ እያሉ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው። አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ እንዲሁም አንድ ለኤልያስ፣ ሦስት መጠለያዎችን እንሥራ” አለው። ጴጥሮስ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።

ጴጥሮስ እየተናገረ እያለ፣ ብሩህ ደመና መጥቶ ከበባቸውና ከደመናው ድምፅ፣ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት” አለ። ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ፈሩና መሬት ላይ ወደቁ።

ያኔ ኢየሱስ ዳሰሳቸውና፣ “አትፍሩ፣ ተነሡ” አላቸው። ዙሪያቸውን ሲያዩ ከኢየሱስ በቀር ማንም አልነበረም።

ኢየሱስና ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ከተራራው ወረዱ። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ “በዚህ ስለ ሆነው ነገር ገና ለማንም አትናገሩ። እኔ በቶሎ እሞታለሁ፣ ሕያውም እሆናለሁ። ከዚያ በኋላ ለሰዎች መናገር ትችላላችሁ።”

معلومات ذات صلة

كلمات الحياة - GRN لديها رسائل صوتية تبشيرية فى الاف الغات تحتوى على رسائل الكتاب المقدس الرئيسية عن الفداء والحياة المسيحية.

تحميلات مجانية - هنا يمكنك أن تجد نصوص رسائل GRN الرئيسية فى عدة لغات، بالإضافة إلى صور ومواد أخرى مرتبطة، متوفرة للتحميل.

مكتبة GRN الصوتية - المواد التبشيرية و التعليمية للكتاب المقدس الملائمة لإحتياجات الناس و ثقافاتهم متاحة فى أشكال و أنماط عديدة.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons