unfoldingWord 09 - እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

unfoldingWord 09 - እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

إستعراض: Exodus 1-4

رقم النص: 1209

لغة: Amharic

الجماهير: General

فصيل: Bible Stories & Teac

الغرض: Evangelism; Teaching

نص من الإنجيل: Paraphrase

حالة: Approved

هذا النص هو دليل أساسى للترجمة والتسجيلات فى لغات مختلفة. و هو يجب ان يعدل ليتوائم مع اللغات و الثقافات المختلفة لكى ما تتناسب مع المنطقة التى يستعمل بها. قد تحتاج بعض المصطلحات والأفكار المستخدمة إلى شرح كامل أو قد يتم حذفها فى ثقافات مختلفة.

النص

ዮሴፍ ከሞተ በኋላ ዘመዶቹ በሙሉ በግብፅ ቆዩ። እነርሱና ዘሮቻቸው ለብዙ ዓመታት እዚያ መኖራቸውን ቀጠሉ፤ ብዙ ልጆችንም አፈሩ፤ እነርሱ እስራኤላውያን ተብለው ተጠሩ።

ከመቶዎች ዓመታት በኋላ የእስራኤላውያን ቊጥር እየበዛ መጣ። ግብፃውያንም ዮሴፍንና እነርሱን ለመርዳት ያደረገውን ሁሉ ዘነጉ። እስራኤላውያን እየበዙ በመምጣታቸው ግብፃውያን ፈሯቸው። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ግብፅን ያስተዳድር የነበረው ፈርዖን እስራኤሎችን ለግብፃውያን ባሪያዎች አደረጓቸው።

ግብፃውያን እስራኤላውያንን የግንብ ሥራ እንዲሠሩ፣ ከተማውን ሁሉ እንዲገነቡ በማድረግ በኃይል ያስገድዷቸው ነበር። ከባድ ሥራ ሕይወታቸውን አስቸጋሪ አደረገው። እግዚአብሔር ግን ባረካቸው ብዙ ልጆችም ነበሯቸው።

ፈርዖን እስራኤላውያን ብዙ ሕፃናት እንዳሏቸው አየ፤ ስለዚህ ፈርዖን ከእስራኤላውያን ወንዶች ልጆች ሲወለዱ አባይ ወንዝ ውስጥ በመወርወር እንዲገድሉ ሕዝቡን አዘዘ።

አንዲት እስራኤላዊት ሴት ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርሷና ባለቤቷ የቻሉትን ያህል ልጁን ደበቁ።

የልጁ ወላጆች ልጁን ሊደብቁት ባልቻሉ ጊዜ ልጁን በሚንሳፈፍ ቅርጫት ውስጥ አድርገው በአባይ ወንዝ ዳር ባለው ቄጤማ ፊት ለፊት እንዳይገደል ሊያድኑት ወንዙ ላይ ለቀቁት። ታላቅ እህቱም የሚሆንበትን ለማየት በቅርብ ትከታተለው ነበር።

የፈርዖን ሴት ልጅ ቅርጫት አየችና በውስጡ ያለውን ተመለከተች። ሕፃኑን ባየች ጊዜ እንደ ልጇ አድርጋ ወሰደችው። እርሷም ልጁን የምትንከባከብ እስራኤላዊት ሴት ቀጠረች። የቀጠረቻትም ሴትዮ የገዛ ልጁ እናት መሆኗን ሳታውቅ ነበር። ልጁም ሲያድግና የናቱን ጡት መጥባት ባቆመ ጊዜ ሴትዮዋ ወደ ፈርዖን ልጅ መለሰችው ስሙንም “ሙሴ” ብለው ጠሩት።

አንድ ቀን ሙሴ ባደገ ጊዜ አንድ ግብፃዊ እስራኤላዊ የሆነን ባሪያ ሲመታው አየ ሙሴም እስራኤላዊ ወገኑን ሊያድነው ሞከረ።

ሙሴ ማንም የማያይ መስሎት ግብፃዊውን ገድሎ ቀበረው። ነገር ግን ሙሴ ያደረገውን አንድ ሰው አይቶታል።

ሙሴ ያደረገውን ፈርዖን በሰማ ጊዜ ሊገድለው ሞከረ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ወታደሮች ነፍሱን ወደሚያድንበት ከግብፅ ወደ ምድረ በዳ ሸሸ።

ከግብፅ ሩቅ በሆነ ምድረ በዳ ሙሴ የበጐች እረኛ ሆነ። ከዚያም አገር ሚስት አግብቶ ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደ።

አንድ ቀን ሙሴ በጐቹን እየጠበቀ ሳለ እሳት የሚነድበት ቊጥቋጦ ተመለከተ ይሁን እንጂ ቊጥቋጦው አልተቃጠለም፤ ሙሴም በደንብ ለማየት ወደ ቊጥቋጦው ጠጋ አለ። ወደሚቃጠለው ቊጥቋጦ ጠጋ ሲል የእግዚአብሔር ድምፅ “ሙሴ በቅዱስ ስፍራ ቆመሃልና ከእግርህ ጫማህን አውልቅ” አለው።

እግዚአብሔርም አለ “የሕዝቤን መከራ አይቻለሁና ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ እስራኤልንም ከግብፅ ባርነት ነጻ ታወጣቸዋለህ። ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ተስፋ የሰጠኋቸውን የከነዓንን ምድር እሰጣቸዋለሁ።”

ሕዝቡ ማንላከህ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርምሙሴን “እኔ ያለሁና የምኖር ነኝ ስለዚህ‘ያለና የሚኖር’ ልኮኛልብለህ ንገራቸው” አለው።

ሙሴ ስለ ፈራ ወደ ፈርዖን መሄድ አልፈለገም። ምክንያቱም የንግግር ችሎታ የለኝም ብሎ በማሰቡ ነበር። ስለዚህም እግዚአብሔር የሙሴን ወንድም አሮንን አብሮት እንዲሄድና ሙሴን እንዲረዳው ላከው። እግዚአብሔር ሙሴንና አሮንን ፈርዖን ሕዝቡን አለቅም በሚል ልቡን ሊያደነድን እንደሚችል አስጠነቀቃቸው።

معلومات ذات صلة

كلمات الحياة - GRN لديها رسائل صوتية تبشيرية فى الاف الغات تحتوى على رسائل الكتاب المقدس الرئيسية عن الفداء والحياة المسيحية.

تحميلات مجانية - هنا يمكنك أن تجد نصوص رسائل GRN الرئيسية فى عدة لغات، بالإضافة إلى صور ومواد أخرى مرتبطة، متوفرة للتحميل.

مكتبة GRN الصوتية - المواد التبشيرية و التعليمية للكتاب المقدس الملائمة لإحتياجات الناس و ثقافاتهم متاحة فى أشكال و أنماط عديدة.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?