unfoldingWord 05 - የተስፋው ልጅ

unfoldingWord 05 - የተስፋው ልጅ

إستعراض: Genesis 16-22

رقم النص: 1205

لغة: Amharic

الجماهير: General

الغرض: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

حالة: Approved

هذا النص هو دليل أساسى للترجمة والتسجيلات فى لغات مختلفة. و هو يجب ان يعدل ليتوائم مع اللغات و الثقافات المختلفة لكى ما تتناسب مع المنطقة التى يستعمل بها. قد تحتاج بعض المصطلحات والأفكار المستخدمة إلى شرح كامل أو قد يتم حذفها فى ثقافات مختلفة.

النص

ከዐሥር ዓመታት በኋላ አብራምና ሦራ ከነዓን ደረሱ፣ እስከዚህ ድረስ ልጅ አልነበራቸውም። ስለዚህም የአብራም ሚስት ሦራ እንዲህ አለችው “እግዚአብሔር ልጆች እንዳይኖሩኝ ስለከለከለኝና እኔም ስላረጀሁ አገልጋዬ አጋር ይህችትልህ አግባት ለኔም ልጅ ትውለድለኝ” አለችው።

ስለሆነም አብራም አጋርን አገባት። አጋርም ወንድ ልጅ ወለደች። አብራምም “እስማኤል” ሲል ስም አወጣለት፤ ይሁን እንጂ ሦራ በአጋር ቀናችባት፤ እስማኤል ዐሥራ ሦስት ዓመት ሲሆነው እግዚአብሔር አብራምን እንዲህ አለው።

እግዚአብሔርም አብራምን“እኔ ኤልሻዳይ አምላክ ነኝ ካንተ ጋር ኪዳን እገባለሁ” አለው። አብራምምበግምባሩ መሬት ላይ ተደፋ እግዚአብሔርም አብራምንአለው “አንተ የብዙ ሕዝቦች አባት ትሆናለህ። የከነዓንን ምድር ለአንተና ለዘሮችህ ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ እኔም ለዘላለም አምላካቸው እሆናለሁ አንተም በቤተ ሰብህ የሚገኘውን ወንድ ሁሉ ግረዘው” አለው።

እግዚአብሔርም “ሚስትህ ሦራ ወንድ ልጅ ትወልዳለች እርሱም የተስፋው ልጅ ይሆናል ስሙን ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ኪዳኔንም ከእርሱ ጋር አደርጋለሁ። እርሱም ታላቅ ሕዝብ ይሆናል። እስማኤልንም ታላቅ ሕዝብ አደርገዋለሁ፤ ይሁን እንጂ ኪዳኔ ከይስሐቅ ጋር ይሆናል” አለው። እግዚአብሔርም የአብራምን ስም “አብርሃም” ሲል ለወጠለት ትርጓሜውም “የብዙዎች አባት” ማለት ነው። እግዚአብሔር የሦራንም ስም “ሣራ” ሲል ለወጠላት ትርጓሜውም “የብዙዎች እናት” ማለት ነው።

በዚያኑ ዕለት አብርሃም በቤተ ሰቡ የሚኙትን ወንዶች ሁሉ ገረዘ። ከዓመት በኋላ አብርሃም 100 ዓመት ሲሆነውና ሣራ 99 ዓመት በሆናት ጊዜ ለአብርሃም ወንድ ልጅ ወለደችለት እግዚአብሔርም እንዳላቸው “ይስሐቅ” ሲሉ ስም አወጡለት።

ይስሐቅ ወጣት በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር የአብርሃምን እምነት እንዲህ ሲል ፈተነው፤ “አንዱን ልጅህን ውሰድና ለኔ መሥዋዕት አድርገህ አቅርብልኝ” አለው፤ እንደ ገና አብርሃም እግዚአብሔርን ታዘዘና ልጁን ሊሠዋው አዘጋጀ።

አብርሃምና ይስሐቅ መሥዋዕት ወደሚደረግበት ስፍራ መጓዝ እንደ ጀመሩ ይስሐቅ አባቱን “አባቴ ሆይ ለመሥዋዕት ማቅረቢያ እንጨቱ ይኸውና በጉ ግን የታለ?” ሲል ጠየቀ። አብርሃምም “ልጄ ሆይ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል” ሲል መለሰለት።

ወደ መሥዋዕት ማቅረቢያ ቦታ እንደ ደረሱ አብርሃም ልጁን ይስሐቅን አስሮ በመሠዊያው ላይ አጋደመው። አብርሃምም ልጁን ለማረድ እጁን ዘርግቶ ቢላዋውን አነሣ፤ እግዚአብሔር “ተው በልጁ ላይ ምንም ጉዳት አታድርስበት እንደምትፈራኝና አንድያ ልጅህን ሳስተህ ለኔ እንዳልከለከልከኝ አሁን አውቄአለሁ አለው።

በአቅራቢያው አብርሃም በቊጥቋጦ ውስጥ የታሰረ በግ አየ። እግዚአብሔር በይስሐቅ ፋንታ ለመሥዋዕት የሚሆን በግ አዘጋጅቶ ነበር። አብርሃምም በደስታ በጉን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።

እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፣ “አንድያ ልጅህን ሳይቀር ያለህን ሁሉ ልትሰጠኝ ፍቃደኛ ነበርህና ልባርክህ ቃል እገባለሁ። ዘሮችህ ከሰማይ ክዋክብት ይልቅ ይበዛሉ እኔን ስለ ታዘዝከኝ የዓለም ሕዝቦች ሁሉ ባንተ ይባረካሉ።”

معلومات ذات صلة

كلمات الحياة - GRN لديها رسائل صوتية تبشيرية فى الاف الغات تحتوى على رسائل الكتاب المقدس الرئيسية عن الفداء والحياة المسيحية.

تحميلات مجانية - هنا يمكنك أن تجد نصوص رسائل GRN الرئيسية فى عدة لغات، بالإضافة إلى صور ومواد أخرى مرتبطة، متوفرة للتحميل.

مكتبة GRN الصوتية - المواد التبشيرية و التعليمية للكتاب المقدس الملائمة لإحتياجات الناس و ثقافاتهم متاحة فى أشكال و أنماط عديدة.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons