unfoldingWord 46 - ጳውሎስ ክርስቲያን ሆነ

unfoldingWord 46 - ጳውሎስ ክርስቲያን ሆነ

إستعراض: Acts 8:1-3; 9:1-31; 11:19-26; 13-14

رقم النص: 1246

لغة: Amharic

الجماهير: General

فصيل: Bible Stories & Teac

الغرض: Evangelism; Teaching

نص من الإنجيل: Paraphrase

حالة: Approved

هذا النص هو دليل أساسى للترجمة والتسجيلات فى لغات مختلفة. و هو يجب ان يعدل ليتوائم مع اللغات و الثقافات المختلفة لكى ما تتناسب مع المنطقة التى يستعمل بها. قد تحتاج بعض المصطلحات والأفكار المستخدمة إلى شرح كامل أو قد يتم حذفها فى ثقافات مختلفة.

النص

ሳውል እስጢፋኖስን የገደሉት ሰዎች ልብስ ይጠብቅ የነበረ ወጣት ነበረ። በኢየሱስ አላመነም፣ ስለዚህም አማኞችን አሳደደ። ወንዶችንና ሴቶችን እየያዘ ወደ እስር ቤት ለመጨመር በኢየሩሳሌም ከቤት ወደ ቤት ሄደ። ሊቀ ካህናቱ በዚያ ያሉትን ክርስቲያኖች ይይዝና ወደ ኢየሩሳሌም መልሶ ያመጣቸው ዘንድ ወደ ደማስቆ ከተማ እንዲሄድ ለሳውል ፈቃድ ሰጠው።

ሳውል ወደ ደማስቆ በመጓዝ ላይ እያለ፣ ከሰማይ ብሩህ ብርሃን በዙሪያው ሁሉ አበራ፣ እርሱም ወደ መሬት ወደቀ። አንድ ሰው፣ “ሳውል! ሳውል! ስለምን ታሳድደኛለህ?” ሲለው ሰማ። ሳውል፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ ማን ነህ?” ብሎ ጠየቀ። ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “እኔ ኢየሱስ ነኝ። አንተ እያሳደድከኝ ነው!” ብሎ መለሰለት።

ሳውል በተነሣ ጊዜ፣ ማየት ተሳነው። ወዳጆቹ ወደ ደማስቆ እየመሩ ወሰዱት። ሳውል ለሦስት ቀናት ምንም አልበላም ወይም አልጠጣም።

በደማስቆ ሐናንያ የተባለ ደቀ መዝሙር ነበረ። እግዚአብሔር ለሐናንያ፣ “ሳውል ወዳለበት ቤት ሂድ። እንደ ገና ያይ ዘንድ እጅህን ጫንበት” አለው። ሐናንያ ግን፣ “ጌታ ሆይ፣ ይህ ሰው አማኞችን እንዴት እንዳሳደደ ሰምቼአለሁ” አለ። እግዚአብሔር፣ “ሂድ! ለአይሁዶችና ከሌሎች ሕዝቦች ለሆኑ ወገኖች ስሜን እንዲያውጅ መርጬዋለሁ። ስለ ስሜ ብዙ መከራ ይቀበላል” አለው።

ስለዚህ ሐናንያ ወደ ሳውል ሄደ። እጆቹን ጫነበት፣ እንዲህም አለ፣ “ወደዚህ ስትመጣ የታየህ ኢየሱስ፣ እንደ ገና ታይና በመንፈስ ቅዱስ ትሞላ ዘንድ ወዳንተ ላከኝ።” ሳውል ወዲያውኑ ማየት ቻለ፣ ሐናንያም አጠመቀው። ከዚያ በኋላ ሳውል ምግብ በላ፣ በረታም።

ሳውል ወዲያውኑ፣ “ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው!” በማለት በደማስቆ ለነበሩ አይሁድ መስበክ ጀመረ። አይሁዶች አማኞችን ለማጥፋት የሞከረው ሰው አሁን ደግሞ በኢየሱስ በማመኑ ተደነቁ! ሳውል ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን በማረጋገጥ አይሁዶችን አሳመነ።

ከብዙ ቀናት በኋላ አይሁዶች ሳውልን ለመግደል ዐቀዱ። ይገድሉት ዘንድ በከተማይቱ በሮች የሚጠባበቁትን ሰዎች ላኩ። ነገር ግን ሳውል ስለ ዕቅዱ ሰማ፣ ወዳጆቹም እንዲያመልጥ ረዱት። አንድ ሌሊት በቅርጫት አድርገው በከተማዪቱ ቅጥር አወረዱት። ሳውል ከደማስቆ ካመለጠ በኋላ ስለ ኢየሱሰ መስበኩን ቀጠለ።

ሳውል ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ለመገናኘት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ፣ እነርሱ ግን ፈሩት። በዚያን ጊዜ በርናባስ የተባለ አማኝ ሳውልን ወደ ሐዋርያቱ ወሰደውና ሳውል በደማስቆ እንዴት በድፍረት እንደ ሰበከ ነገራቸው። ከዚያ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ሳውልን ተቀበሉት።

በኢየሩሳሌም ከነበረው ስደት የሸሹ አንዳንድ አማኞች ወደ አንጾኪያ ርቀው ሄዱና ስለ ኢየሱስ ሰበኩ። በአንጾኪያ የነበሩት ብዙዎቹ ሰዎች አይሁዶች አልነበሩም፣ ነገር ግን ለመጀመሪያ ጊዜ፣ በጣም ብዙዎቻቸው ደግሞ አማኞች ሆኑ። በርናባስና ሳውል እነዚህን ዐዳዲስ አማኞች በተጨማሪ ስለ ኢየሱስ ሊያስተምሯቸውና ቤተ ክርስቲያንን ሊያጠናክሩ ወደዚያ ሄዱ። በኢየሱስ የሚያምኑ መጀመሪያ ጊዜ በአንጾኪያ “ክርስቲያኖች” ተባሉ።

አንድ ቀን በአንጾኪያ የነበሩ ክርስቲያኖች እየጾሙና እየጸለዩ እያሉ መንፈስ ቅዱስ፣ “የጠራኋቸውን ሥራ እንዲሠሩ በርናባስንና ሳውልን ለዩልኝ” አላቸው። ስለዚህ በአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ለበርናባስና ለሳውል ጸለዩላቸው፣ እጆቻቸውንም ጫኑባቸው። ከዚያም በሌሎች ብዙ ቦታዎች ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች እንዲሰብኩ ላኩአቸው። በርባናስና ሳውል ከተለያዩ የሕዝብ ወገኖች የሆኑ ሰዎችን አስተማሩ፣ ብዙ ሰዎችም በኢየሱስ አመኑ።

معلومات ذات صلة

كلمات الحياة - GRN لديها رسائل صوتية تبشيرية فى الاف الغات تحتوى على رسائل الكتاب المقدس الرئيسية عن الفداء والحياة المسيحية.

تحميلات مجانية - هنا يمكنك أن تجد نصوص رسائل GRN الرئيسية فى عدة لغات، بالإضافة إلى صور ومواد أخرى مرتبطة، متوفرة للتحميل.

مكتبة GRN الصوتية - المواد التبشيرية و التعليمية للكتاب المقدس الملائمة لإحتياجات الناس و ثقافاتهم متاحة فى أشكال و أنماط عديدة.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?