unfoldingWord 49 - ዐዲሱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን

unfoldingWord 49 - ዐዲሱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን

Raamwerk: Genesis 3; Matthew 13-14; Mark 10:17-31; Luke 2; 10:25-37; 15; John 3:16; Romans 3:21-26, 5:1-11; 2 Corinthians 5:17-21; Colossians 1:13-14; 1 John 1:5-10

Skripnommer: 1249

Taal: Amharic

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bybelaanhaling: Paraphrase

Status: Approved

Skrips is basiese riglyne vir vertaling en opname in ander tale. Hulle moet so nodig aangepas word dat hulle verstaanbaar en relevant is vir elke verskillende kultuur en taal. Sommige terme en konsepte wat gebruik word, het moontlik meer verduideliking nodig of selfs heeltemal vervang of weggelaat word.

Skripteks

አንድ መልአክ ማርያም ለተባለች ድንግል የእግዚአብሔርን ልጅ እንደምትወልድ ነገራት። ስለዚህ እርስዋ ገና ድንግል እያለች ወንድ ልጅ ወለደችና ኢየሱስ ብላ ሰየመችው። ስለዚህ ኢየሱስ አምላክም ሰውም ነው።

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን የሚያረጋግጡ ብዙ ተአምራትን አደረገ። በውሃ ላይ ተራመደ፣ ማዕበልን ጸጥ አደረገ፣ ብዙ በሽተኞችን ፈወሰ፣ አጋንንትን አወጣ፣ ሙታንን አስነሣ፣ እንዲሁም አምስት እንጀራና ሁለት ትንንሽ ዓሣ ከ5,000 ለበለጡ ሰዎች እንዲበቃ አደረገ።

ደግሞም ኢየሱስ ታላቅ መምህር ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆነም በሥልጣን ተናገረ። ራሳችሁን እንደምትወዱ ሌሎችን ሰዎችንም ውደዱ ብሎ አስተማረ።

ደግሞም እርሱ ሀብታችሁን ጨምሮ ማንኛውንም ነገር እንደምትወዱ እግዚአብሔርን መውደድ አለባችሁ ብሎ አስተማረ።

ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት በዓለም ካለ ከማንኛውም ነገር ይልቅ የከበረች ነች አለ። ለማንኛውም ሰው እጅግ በጣም አስፈላጊው ነገር የእግዚአብሔር መንግሥት ወገን መሆን ነው። ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት ከኃጢአታችሁ መዳን አለባችሁ።

ኢየሱስ አንዳንድ ሰዎች ተቀብለውት እንደሚድኑ፣ ሌሎች ግን እንደማይቀበሉት አስተማረ። አንዳንድ ሰዎች እንደ መልካም መሬት ናቸው አለ። የኢየሱስን የምሥራች ተቀብለው ይድናሉ። ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔር ቃል ዘር እንደማይገባበትና ምንም ፍሬ እንደማያፈራ በመንገድ ዳር እንዳለ አለትማ መሬት ናቸው። እነዚያ ሰዎች ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን መልእክት የማይቀበሉና ወደ መንግሥቱ የማይገቡ ናቸው።

ኢየሱስ፣ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን በጣም እንደሚወድ አስተማረ። ይቅር ሊላቸውና ልጆቹ ሊያደርጋቸው ይፈልጋል።

ደግሞም ኢየሱስ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንደሚጠላ ነግሮናል። አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ፣ ኃጢአቱ ዝርያዎቻቸውን ሁሉ ጐዳ። ከዚህ የተነሣ በዓለም ያለ ሁሉም ሰው ኃጢአት ይሠራል ከእግዚአብሔርም ይለያያል። ስለዚህ ሁሉም ሰው የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።

ነገር ግን በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።

በኃጢአታችሁ ምክንያት በደለኞች ናችሁና መሞት ይገባችኋል። እግዚአብሔር በእናንተ ላይ መቈጣት ነበረበት፣ ነገር ግን ቊጣውን በእናንተ ላይ በማፍስስ ፈንታ በኢየሱስ ላይ አፈሰሰው። ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ፣ የእናንተን ቅጣት ተቀበለ።

ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት አላደረገም፣ ነገር ግን የእናንተን ኃጢአትና በዓለም ያለውን የእያንዳንዱን ሰው ኃጢአት ለማስወገድ መቀጣትንና ፍጹም መሥዋዕት ሆኖ መሞትን መረጠ። ኢየሱስ ራሱን ስለ ሠዋ፣ እግዚአብሔር ማንኛውንም ኃጢአት፣ አስከፊ የሆነውን ኃጢአት እንኳ ይቅር ማለት ይችላል።

መልካም ሥራዎች ሊያድኑአችሁ አይችሉም። ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት እንዲኖራችሁ ልታደርጉ የምትችሉት ምንም ነገር የለም። ኢየሱስ ብቻ ኃጢአታችሁን ሊያጥብ ይችላል። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን፣ በእናንተ ፈንታ በመስቀል ላይ መሞቱን እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ብቻ ማመን አለባችሁ።

እግዚአብሔር በኢየሱስ የሚያምነውንና ጌታው አድርጎ የሚቀበለውን ማንኛውንም ሰው ያድናል። ባለ ጠጎች ሆኑ ወይም ድሆች፣ ወንድ ወይም ሴት፣ ሽማግሌ ወይም ወጣት፣ ወይም የትም ብትኖሩ ምንም አይደለም። እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የቅርብ ግንኙነት ሊኖረው ይችል ዘንድ ይወዳችኋል በኢየሱስ እንድታምኑም ይፈልጋል።

ኢየሱስ እንድታምኑና እንድትጠመቁ ይጋብዛችኋል። ኢየሱስ መሲሕ፣ ብቸኛው የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ታምናላችሁ? ኃጢአተኞች መሆናችሁንና እግዚአብሔር ቢቀጣችሁ የተገባ መሆኑን ታምናላችሁ? ኢየሱስ ኃጢአታችሁን ለማስወገድ በመስቀል ላይ መሞቱን ታምናላችሁ?

በኢየሱስና እርሱ ለእናንተ በሠራው ሥራ ብታምኑ፣ እናንተ ክርስቲያኖች ናችሁ! እግዚአብሔር ከሰይጣንና ከጨለማ መንግሥት አውጥቶአችሁ በእግዚአብሔር የብርሃን መንግሥት ውስጥ አድርጎአችኋል። እግዚአብሔር ነገሮችን የምታደርጉበትን አሮጌውንና ኃጢአተኛውን መንገዳችሁን አስወግዶ ዐዲስና ጻድቅ የሆነ የአደራረግ መንገድ ሰጥቶአችኋል።

እናንተ ክርስቲያኖች ናችሁ፣ ኢየሱስ በሠራው ሥራ ምክንያት እግዚአብሔር ኃጢአታችሁን ይቅር ብሎአችኋል። አሁን እግዚአብሔር በጠላቶች ፈንታ የቅርብ ወዳጆች አድርጎ ይቈጥራችኋል።

የእግዚአብሔር ወዳጆችና የጌታ ኢየሱስ አገልጋዮች ከሆናችሁ፣ ኢየሱስ ለሚያስተምራችሁ ነገር ትታዘዛላችሁ። ክርስቲያኖች ብትሆኑም እንኳ፣ አሁንም ኃጢአት ለመሥራት ትፈተናላችሁ። ነገር ግን እግዚአብሔር የታመነ ነውና ኃጢአታችሁን ብትናዘዙ ይቅር እላችኋለሁ ይላል። ኃጢአትን የምትቃወሙበትን ብርታት ይሰጣችኋል።

እግዚአብሔር እንድትጸልዩ፣ ቃሉን እንድታጠኑ፣ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር እንድታመልኩ፣ ያደረገላችሁንም ለሌሎች እንድትነግሩ ይጠይቃችኋል። እነዚህ ነገሮች ሁሉ ከእርሱ ጋር የጠለቀ ግንኙነት እንዲኖራችሁ ይረዱአችኋል።

Verwante inligting

Woorde van Lewe - GRN het oudio-evangelieboodskappe in duisende tale wat Bybelgebaseerde boodskappe bevat oor verlossing en Christelike lewe.

Gratis aflaaie - Hier vind u al die belangrikste GRN boodskap skrips in verskeie tale, plus prente en ander verwante materiaal, wat beskikbaar is om af te laai.

Die GRN Oudiobiblioteek - Evangelistiese en basiese Bybelonderrigmateriaal wat geskik is vir die behoefte en kultuur van die mense in 'n verskeidenheid style en formate.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons