unfoldingWord 22 - የዮሐንስ መወለድ

unfoldingWord 22 - የዮሐንስ መወለድ

Esboço: Luke 1

Número do roteiro: 1222

Idioma: Amharic

Público alvo: General

Tipo: Bible Stories & Teac

Propósito: Evangelism; Teaching

Passagem bíblica: Paraphrase

Estado: Approved

Os roteiros são guias básicos para a tradução e gravação em outros idiomas. Devem ser adaptados de acordo com a cultura e a língua de cada região, para fazê-lo relevante. Certos termos e conceitos podem precisar de uma explicação adicional ou mesmo serem omitidos no contexto de certos grupos culturais.

Texto do roteiro

አስቀድሞ እግዚአብሔር በመላእክቱና በነቢያቱ በኩል ለሕዝቡ ተናግሮ ነበር። ነገር ግን ለእነርሱ ያልተናገረባቸው 400 ዓመታት አለፉ። በድንገት አንድ መልአክ ዘካርያስ ተብሎ ወደሚጠራ ሽማግሌ ካህን ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ይዞ መጣ። ዘካርያስና ሚስቱ ኤልሳቤጥ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ፣ ነገር ግን እርስዋ ልጆችን መውለድ አልቻለችም ነበር።

መልአኩ ዘካርያስን አለው፣ “ሚስትህ ወንድ ልጅ ትወልዳለች። ዮሐንስ ብለህ ተጠራዋለህ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ ይሞላል፣ ሕዝቡንም ለመሲሑ ያዘጋጃል!” ዘካርያስ፣ “ሚስቴና እኔ ልጆችን ለመውለድ በጣም አርጅተናል! ይህ እንደሚሆን እንዴት ዐውቃለሁ?” ብሎ መለሰ።

መልአኩ ለዘካርያስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ ይህን የምሥራች እንዳመጣላችሁ እግዚአብሔር ላከኝ። ስላላመንከኝ፣ ልጁ እስኪወለድ ድረስ መናገር አትችልም።" ወዲያኑ ዘካርያስ መናገር አልቻለም። ከዚያ በኋላ መልአኩ ከዘካርያስ ተለየ። ዘካርያስም ወደ ቤት ተመለሰ ሚስቱም ፀነሰች።

ኤልሳቤጥ የስድስት ወር ነፍሰ ጡር በነበረች ጊዜ፣ ያው መልአክ በድንገት ስምዋ ማርያም ለተባለ ለኤልሳቤጥ ዘመድ ተገለጠ። እርስዋ ድንግል ነበረችና ልታገባ ዮሴፍ ለተባለ ሰው ታጭታ ነበር። መልአኩ፣ “ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። ስሙን ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል ለዘላለምም ገዥ ይሆናል” አለ።

ማርያም “እኔ ድንግል ስለ ሆንኩ፣ ይህ እንዴት ይሆናል?” ብላ መለሰች። መልአኩ እንዲህ ብሎ አብራራ፣ “መንፈስ ቅዱስ ወደ አንቺ ይመጣል፣ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል። ስለዚህ ልጁ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል።” ማርያም አመነች መልአኩ ያለውንም ተቀበለች።

መልአኩ ለማርያም ከተናገረ በኋላ ወዲያወኑ፣ ሄደችና ኤልሳቤጥን ጐበኘቻት። ኤልሳቤጥ የማርያምን ሰላምታ እንደ ሰማች፣ የኤልሳቤጥ ልጅ በሆዷ ውስጥ ዘለለ። ሴቶቹ እግዚአብሔር ስላደረገላቸው ነገር አብረው ሐሤት አደረጉ። ማርያም ኤልሳቤጥን ለሦስት ወራት ከጐበኘቻት በኋላ፣ ማርያም ወደ ቤትዋ ተመለሰች።

ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅዋን ከወለደች በኋላ፣ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ መልአኩ እንዳዘዘው ሕፃኑን ዮሐንስ ብለው ሰየሙት። በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር ለዘካርያስ እንደ ገና እንዲናገር ፈቀደለት። ዘካርያስ እንዲህ አለ፣ “ሕዝቡን ዐስቦአልና እግዚአብሔር ይመስገን! አንተም ልጄ፣ ለኃጢአታቸው ይቅርታ መቀበል እንዴት እንደሚችሉ ለሕዝቡ የምትናገር የልዑል እግዚአብሔር ነቢይ ትባላለህ!”

Informações pertinentes

Palavras de Vida - A GRN tem mensagens evangelísticas em áudio em milhares de idiomas contendo a mensagem bíblica sobre a salvação e a vida cristã.

Downloads gratuitos - Baixe gratuitamente áudios de histórias bíblicas e estudos em milhares de idiomas, além de ilustrações, roteiros e vários outros tipos de material para evangelismo e crescimento da igreja.

Coleção de áudio da GRN - Material evangelístico e de ensino bíblico, adaptado às necessidades e cultura de cada povo em vários estilos e formatos.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?