unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ

unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ

Samenvatting: Matthew 26:57-27:26; Mark 14:53-15:15; Luke 22:54-23:25; John 18:12-19:16

Scriptnummer: 1239

Taal: Amharic

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bijbelse verwijzing: Paraphrase

Toestand: Approved

De scripts dienen als basis voor de vertaling en het maken van opnames in een andere taal. Ze moeten aangepast worden aan de verschillende talen en culturen, om ze zo begrijpelijk en relevant mogelijk te maken. Sommige termen en begrippen moeten verder uitgelegd worden of zelfs weggelaten worden binnen bepaalde culturen.

Tekst van het script

አሁን ጊዜው እኩለ ሌሊት ነው። ሊቀ ካህናቱ ይጠይቀው ዘንድ ወታደሮቹ ኢየሱስን ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤት ወሰዱት። ጴጥሮስ ራቅ ብሎ ከኋላ ተከተላቸው። ኢየሱስን ወደ ቤቱ ባስገቡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ በውጪ ሆኖ እሳት ይሞቅ ነበር።

በቤቱ ውስጥ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለፍርድ አቀረቡት። ስለ እርሱ የዋሹ ብዙ የሐሰት ምስክሮችን አመጡ። ይሁን እንጂ፣ ቃላቸው እርስ በርሱ አልተስማማም፣ ስለዚህ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስ በማንኛውም ነገር በደለኛ መሆኑን ማረጋገጥ አልቻሉም።

በመጨረሻ፣ ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስን በቀጥታ ተመለከተውና፣ ንገረን፣ አንተ መሲሑ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህን?" አለው።

ኢየሱስ፣ “እኔ ነኝ፣ እንዲሁም ከእግዚአብሔር ጋር ተቀምጬና ከሰማይ ስመጣ ታያለህ” አለው። ሊቀ ካህናቱ በቊጣ ልብሱን ቀደደና ወደ ሌሎቹ የሃይማኖት መሪዎች፣ “ተጨማሪ ምስክሮች አያስፈልጉም! የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ሲል ሰምታችሁታል። ፍርዳችሁ ምንድን ነው?” ብሎ ጮኸ።

ሁሉም የአይሁድ መሪዎች፣ “መሞት ይገባዋል!” ብለው ለሊቀ ካህናቱ መለሱለት። ከዚያም ኢየሱስን ፊቱን ሸፈኑት፣ ተፉበት፣ መቱት፣ ዘበቱበትም።

ጴጥሮስ ከቤቱ ውጪ በመጠባበቅ ላይ እያለ የቤት ሠራተኛ የሆነች ልጅ ዐየችውና፣ “አንተም ደግሞ ከኢየሱስ ጋር ነበርክ!” አለችው። ጴጥሮስ እርስዋ የተናገረችውን ካደ። ከዚያ በኋላ ሌላዋ የቤት ሠራተኛ ያንኑ ተናገረች፣ ጴጥሮስም እንደገና ካደ። በመጨረሻ ሕዝቡ “ሁለታችሁም ከገሊላ ስለሆናችሁ አንተ ከኢየሱስ ጋር መሆንህን እናውቃለን” አሉ።

ከዚያም ጴጥሮስ፣ “ይህንን ሰው የማውቀው ከሆነ የእግዚአብሔር መርገም በእኔ ላይ ይሁን! ብሎ ማለ። ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ፣ ኢየሱስም ዘወር አለና ጴጥሮስን ተመለከተው።

ጴጥሮስ ሄደና በምሬት አለቀሰ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ፣ የአይሁድ መሪዎች እንዲሞት በኢየሱስ ላይ እንደ ፈረዱበት ዐየ። ይሁዳ በሐዘን ተሞልቶ ሄደና ራሱን ገደለ።

በነጋታው ማለዳ ላይ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ወደ ሮማው ገዥ ወደ ጲላጦስ አመጡት። ጲላጦስ ኢየሱስን ጥፋተኛ ነህ ብሎ ይፈርድበትና በሞት እንዲቀጣ ያደርጋል ብለው ተስፋ አደረጉ። ጲላጦስ ኢየሱስን፣ “የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” ብሎ ጠየቀው።

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አንተ አልህ፣ ነገር ግን መንግሥቴ ምድራዊ መንግሥት አይደለችም። እንደዚያ ብትሆን ኖሮ፣ አገልጋዮቼ ይዋጉልኝ ነበር። ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ለመናገር ወደ ምድር መጥቼአለሁ። እውነትን የሚወድ ሁሉ እኔን ይሰማኛል።” ጲላጦስ፣ “እውነት ምንድን ነው?” አለ።

ጲላጦስ ከኢየሱስ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሕዝቡ ወጣና፣ “በዚህ ሰው ላይ ምንም በደል አላገኘሁበትም” አለ። የአይሁድ መሪዎችና ሕዝቡ ግን፣ “ስቀለው!” ብለው ጮኹ። ጲላጦስ፣ “በደለኛ አይደለም” ብሎ መለሰላቸው። እነርሱ ግን የበለጠ ጮኹ። ከዚያም ጲላጦስ ለሦስተኛ ጊዜ፣ “በደል የለበትም!” አለ።

ጲላጦስ ሕዝቡ መረበሽ ይጀምራሉ ብሎ ፈራ፣ ስለዚህ ኢየሱስን እንዲሰቅሉት ወታደሮቹን አዘዘ። የሮማ ወታደሮች ኢየሱስን ገረፉትና ቀይ ልብስ አለበሱት፣ እንዲሁም የሾኽ አክሊል በራሱ ላይ አደረጉ። ከዚያም፣ “እነሆ፣ የአይሁድ ንጉሥ!” በማለት ዘበቱበት።

Verwante informatie

Woorden van Leven - GRN beschikt over audio opnamen in duizenden talen. Deze opnamen gaan over het verlossingsplan en het leven als christen.

Vrij te downloaden - Download Bijbelverhalen in audio formaat en Bijbellessen in duizenden talen, afbeeldingen, scripts en andere verwante materialen die geschikt zijn voor evangelisatie en gemeenteopbouw.

De GRN-audiobibliotheek - Evangelisatiemateriaal en basisbijbelonderricht, aangepast aan de behoeften en de cultuur van het volk, in verschillende stijlen en formaten.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?