unfoldingWord 38 - ኢየሱስ ተላልፎ ተሰጠ

unfoldingWord 38 - ኢየሱስ ተላልፎ ተሰጠ

Garis besar: Matthew 26:14-56; Mark 14:10-50; Luke 22:1-53; John 18:1-11

Nomor naskah: 1238

Bahasa: Amharic

Pengunjung: General

Jenis: Bible Stories & Teac

Tujuan: Evangelism; Teaching

Kutipan Alkitab: Paraphrase

Status: Approved

Naskah ini adalah petunjuk dasar untuk menerjemahkan dan merekam ke dalam bahasa-bahasa lain. Naskah ini harus disesuaikan seperlunya agar dapat dimengerti dan sesuai bagi setiap budaya dan bahasa yang berbeda. Beberapa istilah dan konsep yang digunakan mungkin butuh penjelasan lebih jauh, atau diganti atau bahkan dihilangkan.

Isi Naskah

አይሁድ በያመቱ የፋሲካን በዓል ያከብሩ ነበር። ይህም በዓል ከብዙ ምእት ዓመታት በፊት እግዚአብሔር ቅድማያቶቻቸውን በግብፅ ከነበረው ባርነት እንዴት እንዳዳናቸው የሚከበር ነበር። ኢየሱስ መጀመሪያ በይፋ መስበኩንና ማስተማሩን ከጀመረ ከሦስት ዓመት ገደማ በኋላ፣ ይህን ፋሲካ በኢየሩሳሌም ከእነርሱ ጋር ሊያከብር እንደ ፈለገ፣ በዚያም እንደሚገደል ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው።

ከኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ይሁዳ ተብሎ የሚጠራ ሰው ነበር። ይሁዳ የሐዋርያቱ የገንዘብ ከረጢት ኃላፊ ነበር፣ ነገር ግን ገንዘብ ይወድ ነበርና ብዙ ጊዜ ከከረጢቱ ውስጥ ገንዘብ ይሰርቅ ነበር። ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም ከደረሱ በኋላ፣ ይሁዳ ወደ አይሁድ መሪዎች ሄደና ኢየሱስን በገንዘብ አሳልፎ ሊሰጣቸው ተስማማ። ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን የአይሁድ መሪዎች እንደ ካዱና ሊገድሉት ያሤሩ እንደ ነበር ዐወቀ።

የአይሁድ መሪዎች በሊቀ ካህናቱ እየተመሩ፣ ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጣቸው ለይሁዳ ሠላሳ ብር ከፈሉት። ልክ ነቢያት እንደ ተነበዩት ይህ ሆነ። ይሁዳ ተስማማ፣ ገንዘቡንም ይዞ ሄደ። ኢየሱስን እንዲይዙት ሊረዳቸው አጋጣሚ መፈለግ ጀመረ።

በኢየሩሳሌም፣ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ፋሲካን አከበረ። በፋሲካው ምግብ ጊዜ ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ቈረሰ። እንዲህም አለ፣ “እንካችሁ ይህንን ብሉ። ይህ ስለ እናንተ የተሰጠ ሥጋዬ ነው። ይህንን ለመታሰቢያዬ አድርጉት።” በዚህ ዓይነት ኢየሱስ ሥጋው ስለ እርሱ እንደሚሠዋ ነገራቸው።

ከዚያም ኢየሱስ ጽዋን አንሣና፣ “ይህንን ጠጡ። ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የዐዲስ ኪዳን ደሜ ነው። ይህንን በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ለመታሰቢያዬ አድርጉት።”

ከዚያም ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ “ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጠኛል” አላቸው። ደቀ መዛሙርቱ ደነገጡ፣ እንዲህ ያለ ነገር ማን ያደርጋል ብለውም ጠየቁ። ኢየሱስ፣ “ይህንን ቊራሽ እንጀራ የምሰጠው ሰው እኔን አሳልፎ ይሰጠኛል” አለ። ከዚያ በኋላ እንጀራውን ለይሁዳ ሰጠው።

ይሁዳ እንጀራውን ከተቀበለ በኋላ፣ ሰይጣን ገባበት። ይሁዳ ኢየሱስን እንዲይዙ የአይሁድ መሪዎችን ሊረዳቸው ሄደ። ጊዜው ማታ ነበር።

ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ እራት ከበሉ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ሄዱ። ኢየሱስ፣ “ዛሬ ማታ ሁላችሁም ትተዉኛላችሁ። ‘እረኛውን እመታለሁ በጎቹም ሁሉ ይበተናሉ’ ተብሎ ተጽፎአል” አለ።

ጴጥሮስ፣ “ሌሎቹ ሁሉ ቢተዉህ እንኳ፣ እኔ ግን አላደርገውም!” ብሎ መለሰ። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ጴጥሮስን እንዲህ አለው፣ “ሰይጣን ሁላችሁንም ሊወስዳችሁ ይፈልጋል፣ ነገር ግን ጴጥሮስ እምነትህ እንዳይደክም ጸልዬልሃለሁ። እንደዚያም ሆኖ ግን ዛሬ ማታ ዶሮ ከመጮኹ በፊት እንደማታውቀኝ እንኳ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ።”

በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስ፣ “መሞት ቢኖርብኝ እንኳ፣ ከቶ አልክድህም” አለው። ሌሎቹ ደቀ መዛሙርት ሁሉ ይህንኑ አሉ።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደሚባል ቦታ ሄደ። ኢየሱስ ወደ ፈተና እንዳይገቡ እንዲጸልዩ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ከዚያም ኢየሱስ ብቻውን ሊጸልይ ሄደ።

ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ጸለየ፣ “አባቴ ሆይ፣ ቢቻልስ ይህን የመከራ ጽዋ እንዳልጠጣው አድርግ። ነገር ግን የሰዎች ኃጢአት ይቅር የሚባልበት ሌላ መንገድ ከሌለ፣ ፈቃድህ ይሁን።” ኢየሱስ በጣም ታወከ ላቡም እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ። እግዚአብሔር ሊያበረታታው መልአክ ላከ።

ከእያንዳንዱ የጸሎት ጊዜ በኋላ ኢየሱስ ወደ ደቀ መዛሙርቱ ተመላለሰ፣ እነርሱ ግን ተኝተው ነበር። ሦስተኛ በተመለሰ ጊዜ ግን፣ “ተነሡ! አሳልፎ የሚሰጠኝ እዚህ ነው” አለ።

ይሁዳ ከአይሁድ መሪዎች፣ ከወታደሮችና ከብዙ ሕዝብ ጋር መጣ። ሰይፍና ዱላ ይዘው ነበር። ይሁዳ ወደ ኢየሱስ መጣና፣ “መምህር ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን” አለው፣ ሳመውም። ይህም የአይሁድ መሪዎች ማንን እንደሚይዙ ምልክት ነበር። ከዚያም ኢየሱስ፣ “ይሁዳ፣ በመሳም አሳልፈህ ትሰጠኛለህን?” አለ።

ወታደሮቹ ኢየሱስን እንደ ያዙት፣ ጴጥሮስ ሰይፉን መዘዘና የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ ቈረጠ። ኢየሱስ፣ “ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ! ይከላከሉልኝ ዘንድ የመላእክት ሠራዊት እንዲልክልኝ አባቴን መጠየቅ እችላለሁ” አለው። ከዚያም ኢየሱስ የሰውዬውን ጆሮ ፈወሰው። ኢየሱስ ከተያዘ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ሸሹ።

Keterangan terkait

Firman Kehidupan - GRN mempunyai rekaman pesan Injil dalam ribuan bahasa berisikan pesan berdasarkan Alkitab tentang keselamatan dan kehidupan Kristiani.

Unduhan-Unduhan Gratis - Disini anda dapat menemukan semua pesan naskah GRN yang utama dalam beberapa bahasa, ditambah gambar dan materi terkait lainnya yang dapat diunduh.

Perpustakaan Audio GRN - Bahan pengabaran Injil dan pengajaran dasar Alkitab yang sesuai dengan kebutuhan masyarakat dan budaya dalam berbagai macam bentuk dan format.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?