unfoldingWord 07 - እግዚአብሔር ያዕቆብን ባረከ

unfoldingWord 07 - እግዚአብሔር ያዕቆብን ባረከ

Grandes lignes: Genesis 25:27-35:29

Numéro de texte: 1207

Langue: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Objectif: Evangelism; Teaching

Citation biblique: Paraphrase

Statut: Approved

Les scripts sont des directives de base pour la traduction et l'enregistrement dans d'autres langues. Ils doivent être adaptés si nécessaire afin de les rendre compréhensibles et pertinents pour chaque culture et langue différente. Certains termes et concepts utilisés peuvent nécessiter plus d'explications ou même être remplacés ou complètement omis.

Corps du texte

ልጆቹም እንዳደጉ ያዕቆብ ከእናቱ ጋር በቤት መቆየትን ይወድ ነበር። ኤሳው ግን አደን ማደን ይወድ ነበር። ርብቃ ያዕቆብን ትወድደው ነበር፣ ይስሐቅ ግን ኤሳውን ይወድደው ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ኤሳው ከአደን ተመልሶ ሲመጣ በጣም ተርቦ ነበር። ኤሳው ያዕቆብን “እባክህ ካዘጋጀኸው ምግብ ትንሽ ስጠኝ” አለው። ያዕቆብም በመጀመሪያ የብኩርናህን መብት ስጠኝ ሲል መለሰለት። ስለዚህም ኤሳው የብኩርናውን መብት ለያዕቆብ ሰጠው ከዚያም ያዕቆብ ከሠራው ምግብ ሰጠው።

ይስሐቅ በረከቱን ለኤሳው ሊሰጠው ፈለገ።ነገር ግንይህን ከማድረጉበፊት ርብቃና ያዕቆብ ይስሐቅን አታለሉት። ያዕቆብ ኤሳውንመስሎ ወደ ይስሐቅ ቀረበ። ይስሐቅ አርጅቶነበር ማየትም አይችልም ነበር። ስለዚህም ያዕቆብ የኤሳውን ልብሶችለብሶ የፍየልለምድ በአንገቱናበእጁ አድርጎ ወደ ይስሐቅ በመቅረብ ይስሐቅን አታለለው።

ያዕቆብ ወደ ኤሳው መጣና እንዲህ አለው፣ “እኔ ኤሳው ነኝ መጥቻለሁና ልትባርከኝ ትችላለህ” ይስሐቅ የፍየሉን ፀጉር ዳሰሰና የልብሱንም ጠረን አሽትቶ ኤሳው እንደ ሆነ አሰበና ባረከው።

ያዕቆብ የብኵርና መብቱንና በረከቱን አታልሎ ስለ ወሰደበት ኤሳው ያዕቆብን ጠላው አባታቸው ከሞተ በኋላ ሊገድለውም አሰበ።

ነገር ግን ርብቃ የኤሳውን እቅድ ሰማች። ስለዚህም እሷና ይስሐቅ ከዘመዶቹ ጋር እንዲኖር ወደ ሩቅ አገር ያዕቆብን ሰደዱት።

ያዕቆብ ለረዥም ዓመታት ከርብቃ ዘመዶች ጋር ኖረ። በዚያም ጊዜ ትዳር መስርቶ 12 ወንዶች ልጆችና 1 ሴት ልጅ ወለደ። እግዚአብሔርም በጣም አበለጸገው።

በከነዓን ከኖረበት ከሃያ (20) ዓመታት በኋላ ያዕቆብ ከቤተ ሰቡ፣ ከሠራተኞቹና ከመንጋው ሁሉ ጋር ወደ ከነዓን ምድር ለመመለስ ወሰነ።

ኤሳው አሁንም ሊገድለኝ ያስብ ይሆናል ብሎ በልቡ ስላሰበ ያዕቆብ ፈራ። ስለዚህም የእጅ መንሻ እንዲሆነው የብዙ ከብቶች መንጋ ስጦታ አድርጎ ለኤሳው ላከለት። ከብቶቹን ያመጡለት የያዕቆብ አገልጋዮች ኤሳውን “አገልጋይህ ያዕቆብ እነዚህን ከብቶች ልኮልሃል እርሱም በቅርቡ ይመጣል” አሉት።

ኤሳው ግን ቀድሞውኑ ያዕቆብን ይቅር ብሎት ስለ ነበር ዳግም ለመገናኘት ደስተኞች ነበሩ። ያዕቆብ በከነዓን ምድር በሰላም ኖረ፤ ከዚያም ይስሐቅ ሞተ ያዕቆብና ኤሳው ቀበሩት እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባለት የቃል ኪዳኑ ተስፋ አሁን ከይስሐቅ ወደ ያዕቆብ ተላለፈ።

Informations reliées

Mots de Vie - GRN présente des messages sonores évangéliques dans des milliers de langues à propos du salut et de la vie chrétienne.

Téléchargements gratuits - Ici vous allez trouver le texte pour les principaux messages GRN en plusieurs langues, plus des images et autres documents prêts à télécharger

La collection d'Enregistrements de GRN - Matériel d'évangélisation et d'enseignement biblique de base adapté aux besoins et à la culture du peuple, dans une variété de styles et de formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?